August 27, 2021

ምስሎቹ በህውሃት ሃይሎች ተመተው የወደቁ ድሮኖችን ያሳያሉ?

HAQCHECK

ሀቅቼክ መረጃውን መርምሮ ሀሰት ብሎታል።

Avatar: Rehobot Ayalew
By Rehobot Ayalew

Rehobot is a lead fact-checker at HaqCheck. She is a trainer and a professional who works in fact-checking and media literacy.

By Kirubel Tesfaye

Kirubel works as a fact-checker at Addis Zeybe for HaqCheck. He is interested in learning and expanding his writing and journalistic skills.

ምስሎቹ በህውሃት ሃይሎች ተመተው የወደቁ ድሮኖችን ያሳያሉ?

አንድ የትዊተር ገጽ በሰኔ 20 ፣ 2013 ዓ.ም ባጋራው ትዊት (የትዊተር ልጥፍ) በአማራ ክልል አከባቢ ተመተው የወደቁ ወታደራዊ ድሮኖች ስለመኖራቸው ሁለት ምስሎችን አያይዞ ልጥፏል። ከምስሎቹ ጋር ተያይዞ የተጻፈው ጽሁፉ “ከትግራይ ሀይሎች ባገኘውት መረጃ መሰረት የፌደራሉ መንግስት ሲጠቀምባቸው የነበሩ ድሮኖች በአማራ ክልል የግጭት ቀጠና ውስጥ በህውሀት ሃይሎች ተሞቶ ወድቋል” ሲል ይነበባል።

የትዊተር መረጃውም ይህ ጽሁፍ እስከተጻፈበት ጊዜ ድረስ ከ 375 ጊዜ በላይ ተጋርቷል። ሀቅቼክ መረጃውን መርምሮ ሀሰት ብሎታል።

ከህዳር 2012 ዓ.ም ጀምሮ በፌደራል መንግስቱ እና በሕውሃት ሀይሎች መካከል ወራት ያስቆጠረ ግጭት እየተካሄደ ነው። ጦርነቱ የጀመረው ትግራይ በሚገኘው የሰሜን ዕዝ ወታደራዊ ካምፕ ላይ ህወሀት ጥቃት ከፈጸመ በኋላ እንደሆነ የፌደራል መንግስቱ ተናግሯል። በግጨቱም ሂደት፤ የአየር ሀይሉ በዘመናዊ ድሮኖች (ሰው አልባ አውሮፕላኖች) ብቃት ያለው መሆኑን፤ እነዚህ ድሮኖችም በጦርነቱ ላይ ጥቅም ላይ እየዋሉ እንደሆኑ ከፍተኛ የመከላከያ ባለስልጣናት በተለያዩ ጊዜያት አሳውቀዋል። 

ሆኖም ሪቨርስ ኢሜጅ የተባለው የምስል ማጣሪያ እንደሚያሳየው ምስሎቹ አሁን በሰሜኑ የኢትዮጵያ ክፍል ካለው ወቅታዊ ሁኔታ ጋር ምንም ግንኙነት የላቸውም።

የመጀመሪያው ምስል ለመጀመሪያ ጊዜ የተጋራው ጥቅምት 10 ፣ 2013 ዓ.ም ሲሆን ምስሉ የሚያሳየው በአርሳክ ጦር አማካኝነት ጥቃት የደረሰበትን የቱርክ ሰው አልባ አውሮፕላን ነው። ምስሉ የተወሰደው በ2012 ዓ.ም በነበረው በናጎርኖ-ካራባክ ጦርነት ወቅት እንደሆነ ተገልፁአል።

 ትክክለኛ ምስል 1

ሁለተኛው ምስል ለመጀመሪያ ጊዜ የተጋራው ሃምሌ ፣ 9 2012 ዓ.ም ሲሆን ምስሉ የሚያሳየው በአዘርባጃን እና በአርሜንያ መካከል በነበረው ጦርነት በሃገራቱ ሰሜናዊ ድንበር አካባቢ በአዘርባጃን ጦር ተመቶ የወደቀ የአርሜንያ ድሮን ነው።

ትክክለኛ ምስል 2

ስለሆነም የትዊተር ልጥፉ በሕውሃት ሃይሎች ተሞቶ የወደቀን የኢትዮጵያ ድሮን የማያሳይ በመሆኑ ሀቅቼክ መረጃውን ሀሰት ብሎታል።