August 27, 2021

ምስሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ በሰሜን ኮሪያ ያደረጉትን ጉብኝት ያሳያል?

HAQCHECK

ሀቅቼክ መረጃውን አጣርቶ ምስሎቹ የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር በሰሜን ኮሪያ ጉብኝት ማድራጋቸውን የማያሳይ በመሆኑ መረጃውን ሀሰት ብሎታል።

Avatar: Naol Getachew
By Naol Getachew

Naol is a journalist and fact-checker at Addis Zeybe for HaqCheck. He is a professional working in the fields of fact-checking, journalism, online storytelling, and translation.

By Kirubel Tesfaye

Kirubel works as a fact-checker at Addis Zeybe for HaqCheck. He is interested in learning and expanding his writing and journalistic skills.

ምስሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ በሰሜን ኮሪያ ያደረጉትን ጉብኝት ያሳያል?

ከ106,708 በላይ ተከታይ ያለው የፌስቡክ ገፅ ነሃሴ ፣ 19 2013 ዓ.ም ባጋራው የፌስቡክ ልጥፍ “ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ለሁለት ቀናት የስራ ጉብኝት ወደ ሰሜን ኮሪያ አቅንተዋል” ከሚል ጽሁፍ ጋር ሁለት ምስሎችን አያይዞ አጋርቷል።

ይህ ጽሁፍ እስከተጻፈበት ጊዜ ድረስ ልጥፉ ከ730 ጊዜ በላይ ተጋርቷል። ሀቅቼክ ልጥፉን መርምሮ ሀሰት ብሎታል።

ከሳምንት በፊት ነሃሴ ፣ 12 2013 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ከአማካሪዎቹ ጋር በመሆን ለአንድ ቀን የስራ ጉብኝት ወደ ቱርክ አቅንቶ የቱርኩን ፕሬዝዳንት ረሲፕ ጣይብ ኤርዶጋንን አግኝተው ነበር። በውይይታቸውም በሁለትዮሽ እና በቀጠናው ጉዳይ ላይ ተወያይተው በመጨረሻም  የወታደራዊ ስምምነት ማድረጋቸው ተነግሯል።  

ይህንን ተከትሎም ሀቅቼክ በፌስቡክ ልጥፉ ላይ የያያዙትን ምስሎች በሪቨርስ ኢሜጅ በተባለው የምስል መፈለጊያ ተመልክቷል። ምስሎችሁ ለመጀመሪያ ጊዜ የተለጠፉት በኢትዮጵያ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ከሁለት አመት በፊት በተመሳሳይ ቀን (ነሃሴ 20 ፣ 2011 ዓ.ም) ነበር። ምስሎቹም የተወሰዱት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ለሁለት ቀናት ይፋዊ የስራ ጉብኝት ወደ ደቡብ ኮሪያ አቅንተው ከደቡብ ኮሪያ ፕሬዝደንት፤ ሙን ጄ ጋር በተገናኙበት ወቅት ነበር። 

ትክክለኛ ምስል

ምስል፡ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በ 2011 ዓ.ም ወደ ደቡብ ኮሪያ ባቀኑበት ጊዜ የተወሰደ።

ከዚህ በተጨማሪም ነሃሴ ፣ 20 2013 ዓ.ም የደቡብ ሱዳኑን ፕሬዝደንት ሳልቫ ኪር ማያርዲት ወደ እኢትዮጵያ በመጡበት ጊዜ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በአዲስ አበባ አቀባበል አድርገውላቸዋል። ይህም ጠቅላይ ሚንስተሩ ለስራ ጉብኝት ከሀገር እንዳልወጡ ያሳያል። ይህ ጽሁፍ እስከ ተጻፈበት ጊዜ ድረስ ስለ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሰሜን ኮሪያ ጉዞ ከሚመለከታቸው አካላት የወጣ ምንም መረጃ የለም። 

ስለሆነም ሀቅቼክ መረጃውን አጣርቶ ምስሎቹ የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር በሰሜን ኮሪያ ጉብኝት ማድራጋቸውን የማያሳይ በመሆኑ መረጃውን ሀሰት ብሎታል።