መስከረም 30 ፣ 2014

ሀሰት፡ምስሉ አሜሪካ በቅርቡ ለኢትዮጵያ የሰጠችውን የወታደራዊ እርዳታን አያሳይም

HAQCHECK

ምስሎቹ አሜሪካ በቅርቡ ለኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ያደረገችውን ድጋፍ እንደማያሳዩ ተረጋግጧል።

Avatar: Hagos Gebreamlak
ሓጎስ ገብረኣምላኽ

A fact-checker at HaqCheck, he has worked for Fortune as a reporter previously.

ኪሩቤል ተስፋዬ

Kirubel works as a fact-checker at Addis Zeybe for HaqCheck. He is interested in learning and expanding his writing and journalistic skills.

ሀሰት፡ምስሉ አሜሪካ በቅርቡ ለኢትዮጵያ የሰጠችውን የወታደራዊ እርዳታን አያሳይም

የአሜሪካ መንግስት በቅርቡ ለኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት 2.9 ሚሊዮን ዶላር የሚገመት ወታደራዊ ቁሳቁሶች በእርዳታ መልክ ድጋፍ አደረገች በማለት አንድ የፌስቡክ ልጥፍ መስከረም 26፣ 2014 ዓ.ም አጋርቶ ነበር። ልጥፉ የተሽከርካሪ መኪኖችን የሚያሳይ ሁለት ምስሎችን አያይዟል። ድጋፉ የተደረገው ኢትዮጵያ በሶማሊያ አካባቢ የሚንቀሳቀሰውን የአልሸባብን እና ሌሎች የአሸባሪ ቡድኖችን ለመከላከል ለሚደረገው ጥረት መሆኑን አያይዞ ጽፏል።   

ይሁን እንጂ ምስሎቹ አሜሪካ በቅርቡ ለኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ያደረገችውን ድጋፍ እንደማያሳዩ ተረጋግጧል። በመሆኑም ልጥፉ ሀሰት ነው።  

የአሜሪካ መንግሰት ለኢትዮጵያ እርዳታ ከሚያደርጉ አካላት በቀዳሚነት ይጠቀሳል። ኢትዮጵያ ለአሜሪካ በንጉሳዊ አገዛዝ ጊዜ ፤ በቀዝቃዛው ጦርነት ጊዜ እንዲሁም ከመስከረም 11 ጥቃት በኃላ ዋና ስትራቴጂካዊ አጋር ሆና ቆይታለች። ኢትዮጵያም አሜሪካ በሶማሊያ የሚገኘውን አልሸባብን እና አሸባሪ ድርጅቶችን እንቅስቃሴ በመቆጣጠር በምታደርገው እርምጃ ዋነኛ አጋር ነች።

ይሁን እንጂ የተለጠፉት ምስሎች አሜሪካ በቅርቡ ለኢትዮጵያ የሰጠችውን የወታደራዊ ቁሳቁሶች አያሳይም። ምስሉ የሚያሳየው ከአመት በፊት አሜሪካ ለኢትዮጵያ ያደረገችውን የወታደራዊ መገልገያ መሳሪያዎች ድጋፍ ነው። 

በምስሉ ላይ የሚታዩት መኪኖች እና አምቡላንሶች በመስከረም 19፣ 2013 ዓ.ም በአሜሪካ የመከላከያ ዲፓርትመንት በኩል ለኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት የተበረከተ ነበር። 2.9 ሚልዮን ዶላር የሚያወጣው ይህ ወታደራዊ ድጋፍ በቀጠናው አካባቢ በአልሸባብ አና በሌሎች አሸባሪ ድርጅቶች አማካኝነት በኢትዮጵያ ላይ ሊቃጡ የሚችሉ ጥቃቶችን ለመከላከል ታስቦ ነው። እርዳታውም አምቡላንሶችን ፣ ላንድ ክሩዘር መኪኖችን ፣ ከባድ ጭነት መኪኖችን የተለያዩ መሳሪያዎችን እና ወታደራዊ ስልጠናዎችን ያካተተ ነበር። 

እነዚህ ምስሎች መስከረም 19 ፣ 2013 ዓ.ም መቀመጫውን በተባበሩት አረብ ኤሚሬትስ ባደረገ አል-አይን በተባለ የሚዲያ ተቋም ታትመው ነበር። ምስሉን አና ጽሁፉን ለመመልከት እዚህ ጋር ይጫኑ ። 

ምንም እንኳን ኢትዮጵያ ከአሜሪካ መንግስት የተለያዩ ወታደራዊ ድጋፎችን አግኝታ የነበር ቢሆንም እነዚህ ምስሎች ግን ኢትዮጵያ በቅርቡ ከአሜሪካ ያገኘችውን ወታደራዊ ድጋፎችን አያሳይም።ስለዚህ ሀቅ-ቼክ ልጥፉን መርምሮ እና አገናዝቦ ሀሰት ብሎታል።

አስተያየት