ነሐሴ 18 ፣ 2013

ምስሉ በኢትዮጵያ አየር ሃይል የህወሃት ሃይል ላይ አርምጃ መወሰዱን ያሳያል?

HAQCHECK

ምስሎቹ ከጉዳዩ ጋር ምንም ግንኙነት የሌላቸው ሰለሆኑ ሀቅቼክ መረጃውን ሀሰት ብሎታል።

Avatar: Rehobot Ayalew
ርሆቦት አያሌው

Rehobot is a lead fact-checker at HaqCheck. She is a trainer and a professional who works in fact-checking and media literacy.

ኪሩቤል ተስፋዬ

Kirubel works as a fact-checker at Addis Zeybe for HaqCheck. He is interested in learning and expanding his writing and journalistic skills.

ምስሉ በኢትዮጵያ አየር ሃይል የህወሃት ሃይል ላይ አርምጃ መወሰዱን ያሳያል?

ከ215,000 በላይ ተከታይ ያለው የፌስቡክ ገፅ ነሃሴ 5 2013 ዓ.ም ባጋራው  ልጥፍ ላይ መረጃውን “ሰበር ዜና” በማለት ያጋራ ሲሆን ሙሉ ትስሁፉም “በአማራ ክልል ልዩ ስሙ ገረገራ ትምሕርት ቤት ውስጥ በድብቅ ካንፕ ሰርቶ የመሽገው “የጁንታ ሐይል” ጥቃት ከመፈፀሙ በፊት በአየር ሐይላችን በተወስደ ኦፕሬሽን ሙሉ ለሙሉ ለመደምሰስ ተችሏል።’’ ሲል ይነበባል። በልጥፉ የተጠቀሰችው ገርገራ ከተማ በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን ከላሊበላ 73.5 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የምትገኘው ከተማ ናት።

በመሆኑ ምስሎቹ ከጉዳዩ ጋር ምንም ግንኙነት የሌላቸው ሰለሆኑ ሀቅቼክ መረጃውን ሀሰት ብሎታል።

https://lh5.googleusercontent.com/VavxD4qKXJDTrmq2JLJHjMqG5s4X3lpXZ46EJ45_IPytMLx-02bCICTbK30ZICKO_nX10L4WHrPoH7IYfCJMskJKzDnqebOctevb3Kn070sd7lYljSkeGrCmUCl39MGSnm1NmruU

ይህ ልጥፍ ከህዳር 2013 ጀምሮ በኢትዮጵያ ፌደራል መንግስት እና በትግራይ ህዝብ ነፃ አውጪ ግንባር (ህወሓት) ጦር መካከል እየተካሄደ ያለውን ግጭት ተከትሎ በማህበራዊ ሚዲያ እየተዘዋወሩ ከነበሩት መካከል አንዱ ነው። ጦርነቱ ከተጀመረ ከሶስት ሳምንት በኋላ የፌደራል መንግስት የክልሉን ዋና ከተማ መቀሌን እና አብዛኛዎቹን የክልሉን ክፍሎች ተቆጣጥሯል።

ይሁን አንጂ ጦርነቱ ከተጀመረ ከስምንት ወራት በኋላ የፌዴራሉ መንግሥት ወታደሮቹን ከክልሉ ለማውጣት ወስኛለው በማለት የአንድ ወገን ሰብዓዊ የተኩስ አቁም አዋጅ ማወጁ ተሰምቷል። ይህን ተከትሎ የቀድሞው የክልሉ እና የህወሓት አመራሮች የኢትዮጵያ ሰራዊት ከክልሉ መውጣቱ ተከትሎ  ሰኔ 21 ቀን 2013 የክልሉን ዋና ከተማ እና አብዛኞቹን የክልል ግዛቶች መልሰው ተቆጣጠሩ።

የህወሓት-ሀይሎች ከ መካከለኛው የትግራይ ክፍል እየወጡ ወደ ደቡብ እና ደቡብ ምስራቅ መገስገስ በመጀመራቸው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ትግራይን ፣ አማራ እና አፋር ክልልን በሚዋሰኑ የድንበር አካባቢዎች ግጭቶች መከሰታቸው ተዘግቧል። ሀምሌ 29 በአማራ ክልላዊ መንግስት ሰሜን ወሎ ዞን የላሊበላ ከተማን የህወሓት ሀይሎች  መቆጣጠራቸው ተዘግቧል። ያንን ተከትሎ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ነሐሴ 4 ኢትዮጵያውያን በህወሓት ኃይሎች ላይ በሚደረገው ዘመቻ ላይ እንዲሳተፉ ጥሪ አቅርቧል። በአማራ ክልል የአየር ኃይሉ በህወሓት ጦር ላይ ጥቃት ፈፀመ የሚለው የፌስቡክ ጽሑፍ በእነዚህ ሁኔታዎች ወቅት ተጋርቷል።

ሃቅቼክ ሪቨርስ ኢሜጅ በተባለ የምስል ማጣሪያ ገፅ ምስሉን ፈልጎ፤  ምስሉ ለመጀመሪያ ጊዜ የተለጠፈው ጥር 5 2012 መሆኑን አረጋግጧል። ምስሉ የተወሰደው በወቅቱ በባርሴሎና አቅራቢያ በሰሜን ምስራቅ ስፔን በሚገኝ የፔትሮኬሚካል ፋብሪካ ላይ ከተከሰተ ፍንዳታ ላይ ነው።

የመጀመሪያው ምስል

https://lh6.googleusercontent.com/yUQivJVBze70CP2pTxI0bMvVKdytvTASqFwAXPtEtQTGTVKyqhXI2UNwGnS58bisoHNv0pD44QQzyfwLcgaGajXkJezQblKwDLwVv6pN42B6ieoZlY_lwdpkb6pbUCOg1bOoNVNw

መንግስት በህወሓት ሀይሎች ላይ ጥቃት መጀመሩን የሚገልጹ ዘገባዎች ቢኖሩም ፣ ሃቅቼክ ምስሉ በገረገራ በህወሓት ሀይሎች  ላይ የተፈጸመ ጥቃት አለመሆኑን አረጋግጧል። ስለሆነም ምስሉ ከጉዳዩ ጋር  ምንም ግንኙነት የሌለው በመሆኑ ሀቅቼክ የፌስቡክ ልጥፉን ሀሰት ብሎታል።  

አስተያየት