ከአዲስ አበባ 91.9 ኪሜ ርቀት ላይ ያለች ስምጥ ሸለቆ ውስጥ የምትገኝ ከተማ ነች። ምስራቅ ኢትዮጵያን ከመዲናይቱ ጋር የምታገናኝ የንግድ እና የትራንስፖርት ከተማ ስትሆን የኮንፈረንስ ቱሪዝም መዳረሻ ነች፡፡
ከጥቂት ሺህ ብሮች ጀምሮ እስከመቶ ሰማኒያ ሺህ ብር ድረስ ፊያስ-777 በተባለ ድርጅት ተጭበርብረናል ያሉ ሰዎች በተለያዩ መንገዶች ድምጻቸውን ሲያሰሙ ሰንብተዋል
ከዴሴምበር 2021 እ.ኤ.አ ጀምሮ በካሜሮን ፣ ማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ፣ ኮንጎ፣ ናይጄሪያ ከ1315 በላይ ሰዎች ተይዘው 67 ሰዎች መሞታቸው የአለም ጤና ድርጅት ሪፖርት ያሳያል።
በሰብስቴሽኑ ላይ ብልሽት ሲከሰት የጥገና ቡድኑ ከሻሸመኔ 400 ኪ.ሜ ተጉዞ እስኪደርስ ለቀናት የኤሌክትሪክ ኃይል መቋረጥ ስለሚፈጠር ከፍተኛ የደንበኞችን ቅሬታና ግጭት አስከትሏል
የአካባቢው ህብረተሰብ የንፁህ ውሃ መጠጥ አቅርቦት ጥያቄ ከአዲሱ ፕሮጀክት ጋር ብቻ የሚፈታ እንደሆነ ነዋሪዎችም ሆነ የጉዳዩ ባለድርሻ አካላት ይስማማሉ
የዝርፊያው አጠቃላይ ኪሳራ እየተሰላ እንደሆነ ገልጸው ሁለት የብረት ምሰሶዎች መውደቃቸውንና ሦስተኛው ምሰሶ በሁለቱ መውደቅ ምክንያት መጣመሙን ነግረውናል።
የአዳማ ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት ሕግ ተገዢነት ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ዝናው ደረበ ለአዲስ ዘይቤ እንደተማገሩት የተያዙት እቃዎች ጠቅላላ ዋጋ ግምት 19 ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር ነው፡፡
መንገዱ የተዘጋው በኢትዮጵያ ዋነኛ የወጪ ገቢ ንግድ መስመር ላይ በምትገኘው “አውራ ጎዳና” በተሰኘች አነስተኛ መንደር አካባቢ በተነሳ ግጭት ነው። በግጭቱ ምክንያት ዋና ዋና መንገዶች በመዘጋታቸው አሽከርካሪዎች መንቀሳቀስ አልቻሉም ነበር።
ባሳለፍነው ዓመት በደጋፊዎች እና በቡድኑ ማኔጅመንት መካከል አለመግባባት ካስነሱ ጉዳዮች መሃከል የውጤት ቀውስ ዋነኛው ነው።
የከተማዋ ማዘጋጃ ቤት ከማስተር ፕላን ትግበራ ቁጥጥር ጋር በ17 ቦታዎች ባካሄደው የናሙና ጥናት ዘጠኙ በአግባቡ ጥቅም ላይ ሲውሉ ስምንቱ ከታለመላቸው አገልግሎት ውጭ ውለው መገኘታቸው ታውቋል።
ሞተር ሳይክልን በመጠቀም ሥራቸውን የሚያቀላጥፉ የከተማዋ ነዋሪዎች ለአዲስ ዘይቤ እንደተናገሩት እገዳው በእለታዊ ሥራቸው ላይ ከባድ ተጽእኖ አሳድሯል።