በሶማሊያ ብሄራዊ ጦር ላይ የተጣለውን የጦር መሳሪያ ማዕቀብ ማስነሳት የሽብር ስጋትን ለማስወገድ የሚያግዝ በመሆኑ ማዕቀቡ እንዲነሳ የሚጠይቅ የጋራ መግለጫ ይጠበቃል
በእንጅባራ ከተማ ዓመታዊውን የፈረሰኞች ትርዒት የሚወክልና ለጎብኚዎች ክፍት የሚሆን የፈረስ ትርዒት ማዕከል ለመገንባት ዝግጅት መደረጉን ሰምተናል
የውሃ መያዣ ፕላስቲኩን ሰማያዊ ቀለም የሚሰጠው ጥሬ እቃ መቅረቱ በዓመት 50 ሚልየን ዶላር እንዲቆጠብ ቢያደርግም ለዋጋው መናር ፋብሪካዎች የችርቻሮ ነጋዴዎችን ይወቅሳሉ
በገዢዉ ብልፅግና ፓርቲ አማካኝነት የቀረበዉ የክላስተር አደረጃጀት የመፍትሔ ሀሳብ ህገ መንግስታዊ ስርዓቱን ያልተከተለ እና መንግስት በሚፈለገው መንገድ ብቻ እያስኬደዉ የሚገኝ በመሆኑ “ሊቆም ይገባል” ተብሏል
70 አባላት የሚኖረው የብሔረሰቦች ምክር ቤት የክልሉን ህገመንግስት መተርጎም፣ አጣሪ ጉባኤ ማደራጀት እንዲሁም በአስተዳደር እርከኖች መካከል የሚነሱ ችግሮችን መፍታት ከተሰጡት ስልጣኖች ዋነኞቹ ናቸው
አዲስ ዘይቤ ከሽሬ እና አድዋ ከተማ ነዋሪዎች ባገኘችው መረጃ የኤርትራ ጦር አባላት ከስፍራው ለመውጣት ዝግጅት እያደረጉ እና በተለያዩ ተሽከርካሪዎችም ተጭነው ሲንቀሳቀሱ ተመልክተዋል
በአማራ ክልል እስካሁን በማገልገል ላይ የሚገኙት የጤና ባለሙያዎች ከሰኔ 30 ጀምሮ የቅጥር ኮንትራታቸው እንደሚቋረጥ የሚገልፅ ደብዳቤ ደርሷቸዋል።
በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚከናወነው የላብራቶሪ ምርመራ ቁጥር አነስተኛ ቢሆንም በትላንትናው እለት የተመዘገበው ከ5 ሺህ ሰዎች በላይ በወረርሺኙ መያዝ ከኦሚክሮን ጋር የተያያዘ ሊሆን ይችላል።
የኮቪድ 19 የህክምና ፕሮቶኮሎችን ሳያሟሉ፣ ተገልጋዮችና የህክምና ባለሙያዎች ተገቢውን ጥንቃቄ ሳያደርጉ፣ አስታማሚና ጠያቂዎች ያለ በቂ ጥንቃቄ ከታማሚዎች ጋር እንዲገናኙ የሚፈቅዱ የህክምና ተቋማት መኖራቸውን መስማት አስደንጋጭ ነው።
ከልጅነቱ አንስቶ ለኮምፒዩተር ትምህርት ልዩ ዝንባሌና ተሰጥዖ ስለነበረዉ ገና የ7ኛ ክፍል ተማሪ ሳለ ኮምፒዩተሮችን ፕሮግራም ማድረግ መጀመሩን ይናገራል።
ታዳጊው በቅርብ የሚመለከተውን ችግር ለመፍታት ከገነባቸው ድረ-ገጾች መካከል በኦንላይን የባስ ቲኬት መቁረጫ፣ ኦንላይን መገበያያ ይገኙበታል፡፡
ቅርጾችን እና ሞዴሎችን ለማተም የሚያገለግለው ስሪዲ ማተሚያ ማሽን (3D Printer) በቅርብ ዓመታት ለዓለም የተዋወቀ አዲስ የቴክኖሎጂ ፈጠራ ነው።
የገንዘብ እጥረት ሲያጋጥም ለብሔራዊ ባንክ ቢያሳውቁም ገና አልተፈቀደም፣ መመሪያ አልተሰጠንም የሚል ምላሽ ማግኘታቸው ታውቋል
በባህር ዳር ከተማና አካባቢዋ አትክልትና ፍራፍሬ እንዲያለሙ የተሰጣቸውን መሬት ወደ ሪል ስቴት ተቀይሯል በማለት የመሬት ደላሎች እና ባለቤቶች የመሬት ሽያጩን አጧጡፈውታል
በጮቄ ተራራዎች እና ተክሎች መሀል በወጣቱ አብይ አለም የተመሰረተው 'ሙሉ ኢኮሎጅ መንደር' የዓለም ምርጥ የቱሪዝም መንደር ሆኖ ተመረጧል
ድምጻዊ አህመድ ተሾመ (ዲንቢ) “የትዝታው ፈረስ” በተሰኘው ሙዚቃው ውስጥ እንዲህ ሲል አዚሟል፥ “የሳር ተራው ሲሳይ ያስመሸኝ ካራዳ፣ የድሃ እራት ንፍሮ የብርቅዬ ጓዳ”
ልጅ ሆኜ የቆሎ ተማሪ እያለሁ እርሳቸው የሚተክሉትን ችግኝ ከወንዝ ውሃ እያመጣን በማጠጣት እናግዛቸው ነበር። ተግባሩን ልማድ አድርጌው አሁን ድረስ ችግኝ እተክላለሁ ~መሪጌታ እዝራ በአምላኩ
ወደ ዲዛ ዛፍ ተጠግተው ሲመለከቱ በትልቁ የተቀረፀ አቀራረፅ ቀ.ኃ.ሥ የሚል እና በውል የማይለይ ዓመተ ምህረት ዛፉ ላይ ተቀርፆ ይታያል
በአንዳንድ የአዲስ አበባ ሰፈሮች እስከ ጉልበት የሚደርስ የጎዳና ላይ ጎርፍ ይከሰታል። ታዲያ ይህን የጎዳና ላይ 'ወንዝ' ለመሻገር እግረኞች ገንዘብ ከፍለው በሰው ጀርባ ላይ ታዝለው ሲሻገሩ ማየት አሳዛኝ ትዕይነት ነው።
ሁሉን አቀፍ ሰለማዊ ድርድር ሲካሄድ፣ ተሳታፊ የሚሆኑ አካላት የሚወክሉት ቡድን ፈጽሞታል ተብሎ የሚታመኑትን ጥፋቶችን አምኖ በመቀበል ህዝባዊ ይቅርታ መጠየቅና ካሳ መክፈል ይገባቸዋል።
ቃልኪዳን ችግኞቹን የተከለችባቸው ቦታዎች ከከተማ የራቁ በመሆናቸው ዳግም ሄዳ ለማየት ባትችልም፤ ችግኞቹን ለመንከባከብ ግን ፍላጎት አላት።
የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ከ200 በላይ ፕሮጀክቶች ወደስራ ሊገቡ ነው ቢልም የክልሉ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ፕሮጀክቶቹን በተመለከተ ዕውቅና የለኝም ብሏል፡፡
ብሎክቼይን፣ ሕዝብ በአገሩ አስተዳደር ውሳኔ ላይ አንዳይሳተፍ የነበረውን እንቅፋት ያነሳል።